|
በምርት ዘመኑ የተሻለ ምርት እየተገኘ መሆኑ ተገለፀ
|
|
በምስራቅ ጐጃም ዞን በደብረ ኤልያስ ወረዳ በምርት ዘመኑ 256 ሺህ 679 ኩንታል ብልጫ ያለው ምርት በመመረት ላይ መሆኑንና የአርሶ አደሩ የምርት ማምረት ተግባር ሰፊ በመሆኑ ኮምባይነሮችን እየተጠቀሙ የግብርናና ገጠር ልማት ጽ/ቤት ገለፁ፡፡
የወረዳው ግብርናና ገጠረ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊና ምክትል አስተዳደር የሆኑት አቶ ዘላለም ገላው እንደተናገሩት የዘመኑ የገብርና ስራ እንቅስቃሴ ከ2000/2001 የምርት ዘመን የተሻሻሉ ተሞክሮ የነበራቸውን አርሶ አደሮች ተሞክሮ በሁሉም አርሶ አደሮች ዘንድ ለማስፈፀም በተሰራ የማስፋት ተግባር የተሻለ የምርት ዘመን ነው ብለዋል፡፡
በምርት ዘመኑ በስንዴ በቻ 14 ሺህ 767 ሔክታር መሬት በዘር በመሸፈን 617 ሺህ 424 ኩንታል ምርት ለማግኘት ዕቅድ ተይዞ የነበረ ሲሆን በቁም ሰብል ግምገማ እንደተረጋገጠው 713 ሺህ 328 ኩንታል እንደሚገኝና ከሔክታር እስከ 60 ኩንታል መመራት እንደ ተቻለ ተናግረዋል፡፡
መርጌታ አለነ መሸሻና አርሶ አደር አሳዬ ተገኘ እንደገለፁት የቀበሌው አርሶ አደሮች ከማሳቸው የሰብል ስፋትና የምረት መጨመር መነሻነት ኮምባይነር እንዲመጣላቸው በደስብሰባው ሀሳበ ያቀርቡ እንደነበርና አሁን ግን 3ቱ የእህል ማጨጃና መውቂያ መኪናዎች በመግባታቸው በኩንታል 30 ብር በመክፈል እየሰበሰበ እንደሆኑና በቀጣይም አስርና አስራ አምስት በመሆን በአቅማቸው ለመግዛት ዕቅድ እንዳላቸው አስረድተዋል፡፡